
Ethiopia 2025/26 Harvest Update
The 2025/26 harvest is almost about to begin across Ethiopia, with cherries expected to reach full ripeness at varying times by altitude. Overall, the...
Market updates, education, partnership stories, and everything Ethiopian coffee

The 2025/26 harvest is almost about to begin across Ethiopia, with cherries expected to reach full ripeness at varying times by altitude. Overall, the...

Discover why Ethiopia stands out as the birthplace of coffee with unique geography and hundreds of heirloom varietals.
Latest insights from the world of Ethiopian coffee

The 2025/26 harvest is almost about to begin across Ethiopia, with cherries expected to reach full ripeness at varying times by altitude. Overall, the...

With approximately 11.6 million 60-kg bags forecast and exports nearing 288.2 billion Birr ($200.8 billion), Ethiopia must either transform its irrepl...

Addis Ababa, Ethiopia — November 25, 2025 — Marking a new era for Ethiopia’s coffee industry Specialty Coffee Association of Ethiopia (SCAE) is offici...

Discover why Ethiopia stands out as the birthplace of coffee with unique geography and hundreds of heirloom varietals.
Get the latest market insights, harvest reports, and coffee education delivered to your inbox
Stay updated with the latest announcements, market insights, and industry news from Ethiopia's official coffee and tea regulatory body.

ጥር 30/2018በ2018 ያለፉት ስድስት ወራት ከቡና ወጪ ንግድ 1.3ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡የባለስልጣኑ ምክ/ ዋና ዳ/ር ሻፊ ዑመር እንደገለጹት፤ የቡና ዘርፉን ውጤታማነት ይበልጥ ለማሳደግ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው። እየተመዘገቡ ላሉ ውጤቶች በርካታ ስትራቴጂዎች፣ የምርታማነትና ጥራት ማደግ፣ የገበያ አድማስ ማስፋት እንዲሁም ዲጂታላይዜሽንና ዘመናዊ አሰራሮች መተግበራቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ በምርት መጠንና በጥራት ላይ የተከናወኑ ተግባራት የኢትዮጵያ ቡና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ተፈላጊነት ማሳደጋቸውን ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ ቡና የምትልክባቸውን ሀገራት ቁጥር ወደ 84 ከፍ ማለቱንና በተለይም በምስራቅ እስያ ባሉ ገበያዎች በስፋት ለመሳተፍ የተደረጉ የማስተዋወቅ ስራዎች ውጤታማ ናቸው ፡፡ አ/አደሩን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ አጠቃላይ የቡና ግብይት ሂደቱን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የማዘመን ስራ በስፋት እየተተገበረ እንደሚገኝና ዘርፉን ለማዘመን እየተከናወኑ ካሉ ተግባራት መካከል እያንዳንዱ የቡና ምርት ከየት ጣቢያ እንደመጣ፣ የት መጋዘን እንደገባ እንዲሁም ማን እንደላከው መከታተል የሚያስችል የዲጂታል ስርዓት መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ባለስልጣኑ በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 600 ሺህ ቶን ቡና ለውጪ ገበያ በማቅረብ ሦስት ቢሊየን ዶላር ለማግኘት አቅዶ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አቶ ሻፊ አመልክተዋል።በዚህም በበጀት ዓመቱ ያለፉት ስድስት ወራት 200 መቶ ሺህ ቶን ቡና በመላክ 1 ነጥብ 345 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን ጠቁመዋል፡፡ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት 469 ሺህ ቶን ቡና ለዓለም ገበያ በመላክ 2 ነጥብ 65 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቷ ይታወቃል፡፡ ኢዜአጥር 30/2018በ2018 ያለፉት ስድስት ወራት ከቡና ወጪ ንግድ 1.3ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡የባለስልጣኑ ምክ/ ዋና ዳ/ር ሻፊ ዑመር እንደገለጹት፤ የቡና ዘርፉን ውጤታማነት ይበልጥ ለማሳደግ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው። እየተመዘገቡ ላሉ ውጤቶች በርካታ ስትራቴጂዎች፣ የምርታማነትና ጥራት ማደግ፣ የገበያ አድማስ ማስፋት እንዲሁም ዲጂታላይዜሽንና ዘመናዊ አሰራሮች መተግበራቸውን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡ በምርት መጠንና በጥራት ላይ የተከናወኑ ተግባራት የኢትዮጵያ ቡና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ተፈላጊነት ማሳደጋቸውን ጠቁመው፤ ኢትዮጵያ ቡና የምትልክባቸውን ሀገራት ቁጥር ወደ 84 ከፍ ማለቱንና በተለይም በምስራቅ እስያ ባሉ ገበያዎች በስፋት ለመሳተፍ የተደረጉ የማስተዋወቅ ስራዎች ውጤታማ ናቸው ፡፡ አ/አደሩን የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ አጠቃላይ የቡና ግብይት ሂደቱን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የማዘመን ስራ በስፋት እየተተገበረ እንደሚገኝና ዘርፉን ለማዘመን እየተከናወኑ ካሉ ተግባራት መካከል እያንዳንዱ የቡና ምርት ከየት ጣቢያ እንደመጣ፣ የት መጋዘን እንደገባ እንዲሁም ማን እንደላከው መከታተል የሚያስችል የዲጂታል ስርዓት መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ባለስልጣኑ በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 600 ሺህ ቶን ቡና ለውጪ ገበያ በማቅረብ ሦስት ቢሊየን ዶላር ለማግኘት አቅዶ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አቶ ሻፊ አመልክተዋል።በዚህም በበጀት ዓመቱ ያለፉት ስድስት ወራት 200 መቶ ሺህ ቶን ቡና በመላክ 1 ነጥብ 345 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን ጠቁመዋል፡፡ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት 469 ሺህ ቶን ቡና ለዓለም ገበያ በመላክ 2 ነጥብ 65 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማግኘቷ ይታወቃል፡፡ ኢዜአ
የሻይ ልማት ኢንሼቲቭን ተግባራትን በማጠናከር የገጠር ትራንስፎርሜሽን አጀንዳን ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸየደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን በካፋ ዞን ገዋታ ወረዳ የቦጊንዳ የሻይ ችግኝ ዝግጅት ጣቢያ ከአካባቢው ለተወጣጡ አርሶ አደሮችና የግብርና ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷል። ዓላማው የተዘጋጀውን የሻይ ቅጠል ችግኝን ከተከላ በፊት ከውጪው አየር ጋር በተገቢ ማላመድ፣ የመንከባከብና ከተላመደ በኃላ ወደ አርሶ አደሩ ማሳ በመውሰድ ለመትከል ከማሳ ልየታ እስከ ተከላና ምርት አሰባሰብ ሂደት ላይ ግንዛቤ ለማስጨጥ የተዘጋጀ ስልጠና ነው። በተግባር የተደገፈ ስልጠናው በውሽውሽ የሻይ ልማት ባለሙያ በሆኑት በአቶ ጋዲሳ ተስፋዬ ለሰልጣኞች ተሰጥቷል።በስልጠናው ችግኙን በአግባቡ የማላመድ ሂደቱ በአግባቡ መተግበር የችግኞችን ሞት እንደሚታደግ እንዲሁም ተገቢውን ግብዓትና ጥንቃቄ ማድረግ ለምርታማነት ሚናው የጎላ መሆኑ ተነስቷል ።መድረኩን ያጠቃለሉት የክልሉ ቡና ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አስራት መኩሪያ፣ የገጠር ትራንስፎርሜሽንን ዕውን ለማድረግ በአካባቢው ያለውን ዕምቅ አቅምን በመለየት ወደ ውጤት በመቀየር ከአካባቢው ፍጆታ አልፍ ለማዕከላዊና ውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በብዛትና በጥራት ማምረት እንደሚገባ ተናግረዋል።ከነዚህም አንዱ በክልሉ የተጀመረው የሻይ ቅጠል ኢንሼቲቭ መሆኑን በመጥቀስ በዞኑ ውስጥ ያለው ተስማሚ የአየር ንብረት፣ የዝናብ ስርጭትና ለምና ተስማሚ መሬትን በተገቢው በመጠቀም ለተጠቃሚነት በትኩረት በዕቅድ መስራት አለበት ብለዋል።አክለዉም መንግስት እንደ ቡና ልማት ሁሉ ለሻይ ልማቱ ሥራ ትኩረት በመስጠት ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ያነሱት አቶ አስራት ከሂደት እስከ ውጤት ያለው ድካም የሚጠይቅ በመሆኑ ለተሻለ ውጤት በትዕግሥት መስራት እንደሚገባው አንስተዋል። ለተከላ የሚመረጠው ማሳ ለኢንዱስትሪው የሚመች፤ በኩታ ገጠም በማልማት አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ በቅንጅት መስራት ይገባል ያሉት የክልሉ ቡና ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ ኮጅአብ ናቸው።ስልጠናውን በግብዓትነት በመጠቀም ለአርሶ አደሮች ግንዛቤ በመፍጠር ከዘርፉ ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ጨምረው ተናግረዋል። የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የገዋታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አርጋው ኃይሌ፤ የክልሉ ግብርና ቢሮ በወረዳው የተጀመረው ኢንሼቲቭ ውጤታማ እንዲሆን ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።ስልጠናው ኢንሼቲቩ አድስ እንደመሆኑ መጠን የነበሩ የግንዛቤና የክህሎት ክፍተት እንደሚሸፍን ሰጣኞቹ አንስተዋል።በስልጠናው ላይ የክልሉ ቡና ሻይና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ ኮጅአብን ጨምሮ ተከላ ከሚካሄድባቸው 8 ቀበሌዎች የመጡ የቀበሌ ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የግብርና ባለሙያዎችና የችግኝ ጣቢያ አስተባባሪዎችና የባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

https://birrmetrics.com/eu-acknowledges-tangible-progress-in-ethiopias-coffee-sector-under-deforestation-rules/

ከጉጂ ዞን ባለፉት ስድስት ወራት ከ8 ሺህ 200 ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ ቀርቧልአዶላ፤ ጥር 26/2018 (ኢዜአ)፡- ከኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ8 ሺህ 200 ቶን በላይ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የዞኑ ንግድ ጽህፈት ቤት ገለጸ።የጽህፈት ቤቱ ሀላፊ አሬሩ ዋሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በተያዘው በጀት ዓመት ከዞኑ ከ75 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ ነው፡፡ከዞኑ 12 ወረዳዎች እስካሁን ድረስ 8 ሺህ 233 ቶን ጥራትና ደረጃውን የጠበቀ የቡና ምርት ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን ገልጸዋል፡፡እስካሁን ከቀረበው የቡና ምርት ውስጥ 2 ሺህ 71 ቶን የሚሆነው የታጠበ፤ 6 ሺህ 161 ቶን በላይ ደግሞ የተቀሸረ እና የደረቅ ቡና ምርት እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡በዞኑ ባሉት 350 የደረቀና እሸት ቡና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ጥራት ያለው ምርት ተዘጋጅቶ ለገበያ እየቀረበ መሆኑንም ገልፀዋል።የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ረጋሳ ጦሬ በበኩላቸው፤ በዞኑ 377 ሺህ ሄክታር መሬት በቡና ልማት መሸፈኑን አስታውቀዋል፡፡በየአመቱ በአማካይ ከዞኑ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል በላይ የቡና ምርት እየተሰበሰበ እንደሆነ አመልክተው ዘንድሮ ከፍተኛ ምርት እንደሚጠበቅም ጠቁመዋል።#Ethiopian_News_Agency
